エピソード

  • የጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2025/11/06
    DW Amharic -የዛሬው የዓለም ዜና፤ በአፋር ክልል በትግራይ ሀይሎች መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት ለጥቂት ቀናት ሲካሄድ የቆየ ነው መባሉን፤የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ ከ7ኛው አገር አቀፍ ምርጫ በፊት የሕገመንግሥት ማሻሻያ እንዲደረግ መጠየቃቸው፤አልፋሺር በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ከተያዘች ወዲህ ሰባት ጋዜጠኞች የደረሱበት አለመታወቁን፤ሱዳን፤ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በአሸባሪነት እንዲሰየም መጠየቋን፤ደቡብ አፍሪካ በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ውስጥ ተሳትፈው ከተያዙ ዜጎቿ የድረሱልኝ ጥሪ እንደደረሳት መግለጿን፤እስራኤል ከግብፅ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ላይ የተዘጋ ወታደራዊ ቀጠና ማወጇን ያስቃኛል።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2025/11/05
    የጀርመን ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት 10 ታማሚዎችን በመግደል ጥፋተኛ በተባለች ነርስ ላይ የእድሜ ልክ እስራት ፈረደ። ግለሰቧ 27 ሰዎች ላይም የመግደል ሙከራ በማድረግ ጥፋተኛ ተብላለች። ፈረንሳይ ውስጥ በዛሬው ዕለት አንድ ግለሰብ በመኪና ሆን ብሎ በሰዎች ላይ ባደረሰው ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች ተጎዱ። ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል። የጋዛ ባለሥልጣናት እስራኤል በዛሬው ዕለት የ15 ፍልስጤማውያንን አስከሬን መመለሷን አስታወቁ። ሀማስም ከሁለት ሳምንት በፊት 20 ታጋቾችን እና 21 አስከሬኖችን ለእስራኤል አስረክቧል። የሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸው የኒኩሊየር የጦር መሣሪያ ሙከራ እንደምትጀምር ዛሬ አስታወቁ።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2025/11/03
    በውዝግብ እና ዓመፅ ያታጀበው የታንዛንያ ምርጫ ማሸነፋቸውን ያወጁት ሳምያ ሱሉሑ ሐሰን በዛሬው ዕለት የፕረዚደንትነት ቃለ መሐላ ፈጸሙ። የጀርመን ፕረዚደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር በጋና የ3 ቀናት ጉብኝት ለማድረግ አክራ ገብተዋል። እስራኤል በሊባኖስ በሁለት ቦታዎች በፈጸመችው የአየር ጥቃት 2 ሰዎች መገደላቸውንና 7 መቁሰላቸውን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የእሁድ ጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ. ም የዓለም ዜና
    2025/11/02
    የእሁድ ጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ. ም የዓለም ዜና
    続きを読む 一部表示
    7 分
  • የጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    12 分
  • የጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2025/10/31
    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በኦሮምያ ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በሚገኙ አራት ወረዳዎች በኡትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ላይ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተፈጸሙ ያላቸውን ግድያዎች አወገዘ በታንዛንያ የተካሄደውን ምርጫ ተቃውመው ሰልፍ ከወጡት ውስጥ ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል ሲል፣ የታንዛኒያ ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ አስታወቀ። የተመድ ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን ማወቁን ተናግሯል። የትራምፕ አስተዳደር ዩናይትድ ስቴትስ በየዓመቱ የምትቀበላቸውን ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንደምትቀንስ አስታወቀ
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የዓለም ዜና፤ ጥቅምት 20 ቀን 2018 ሐሙስ
    2025/10/30
    አርስተ ዜና፤ -የኤርትራ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብፅን ለ5 ቀናት ለመጎብኘት ዛሬ ከአስመራ ወደ ካይሮ ተጓዙ። ኢሳያስ ግብፅን የሚጎበኙት የግብጹ ፕሬዝደንት አብዱልፈታሕ አል ሲሲ ባደረጉላቸዉ ግብዣ ነዉ።-በኢትዮጵያ ከመንግሥት ጋር ይሰራል የሚል ትችት የሚቀርብበት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፤ ኢዜማ ፓርቲ፤ ገዥዉ ብልፅግና የመንግሥት ሠራተኞችን በግዳጅ የፓርቲ አባል የማድረግ እርምጃን እንዲያቆም ጠየቀ።-የተመድ በሱዳን ዳርፉር የምትገኘውን ኤል-ፋሸር ከተማን የተቆጣጠረዉን በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ርምጃ በጥብቅ አወገዘ።
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የጥቅምት 19 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2025/10/29
    -የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ባለፈዉ ሚዚያ የመን እስር ቤት ዉስጥ የነበሩ ስደተኞችን መግደሉ የጦር ወንጀል ሊሆን እንደሚችል የመብት ተሟጋቾች አስታወቁ።በጥቃቱ የተገደሉት አብዛኞቹ ኢትዮጵያዉያን ሳይሆኑ እንዳልቀረ ተነግሯል።---የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ኤል ፋሻር በተባለችዉ ከተማ የሚኖሩ ሰላማዊ ሰዎችን መግደሉ ዓለም አቀፍ ተቃዉሞና ዉግዘት አስከትሏል።----ሩሲያ በሁለት ቀናት ልዩነት ዉስጥ የኑክሌር አረር መሸከም የሚችሉ አዳዲስ ሚሳዬልና የዉሐ ዉስጥ ሰዉ አዉልባ አዉሮፕላን ሞከረች።የመሳሪያዎቹን ሙከ,ራ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ተቃዉመዉታል።
    続きを読む 一部表示
    12 分