エピソード

  • DW Amharic የሐምሌ 27 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    2025/08/03
    በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ታጣቂዎች ከ50 በላይ ሰዎችን በጅምላ አገቱ። ሩሲያ በዩክሬን ቁጥጥር ሥር በሚገኙት የዶኔትስክ እና ኼርሶን ግዛቶች በሣምንቱ መገባደጃ በፈጸመችው ድብደባ ሰባት ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት ዛሬ እሁድ አስታወቁ። የፍልስጤም ቀይ ጨረቃ ማኅበር በኻን ዩኒስ በሚገኝ ዋና መሥሪያ ቤቱ ላይ በተፈጸመ ጥቃት አንድ ሠራተኛው ሲገደል ሌሎች ሦስት መቁሰላቸውን አስታወቀ። የአውሮፓ ኅብረት የውጪ ጉዳይ ኃላፊ ካያ ኻላስ በሐማስ እጅ የሚገኘው እስራኤላዊ ታጋች ሁኔታ "አስደንጋጭ" ሲሉ አወገዙ። በምሥራቃዊ ሩሲያ ካምቻትካ ግዛት የሚገኝ እሳተ ገሞራ ከ600 ዓመታት ገደማ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ፈነዳ።
    続きを読む 一部表示
    8 分
  • የሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ/ም የዓለም ዜና
    7 分
  • የሐምሌ 25 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    2025/08/01
    -የኢትዮጵያ መንግሥትና ህወሓት የዳግም ጦርነት ፉከራና ዝግጅታቸዉን እንዲያቆሙ የሚደረገዉ ጥሪና ግፊት እንደቀጠለ ነዉ።ከዚሕ ቀደም ተደጋጋሚ ሙከራ ባደረጉት ሽማግሌዎች ላይ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ጥሪም ታክሎበታል።-----እስራኤል ላስራበችዉ ለጋዛ ሕዝብ የተለያዩ መንግሥታት የምግብና የመድሐኒት ርዳታ ከዓየር እየተጣሉ ነዉ።የአሜሪካዉ ልዩ መልዕክተኛ ደቡባዊ ጋዛን ሲጎበኙ፣ የጀርመን ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ደግሞ የእስራኤል ሰፋሪዎች ፍልስጤማዉያንን መግደል፣ማቁሰልና ማጥቃታቸዉን አዉግዘዋል።-የሩሲያና የቻይና የባሕር ኃይላት የስድስት ቀናት የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ዛሬ ጀመሩ።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓም የዓለም ዜና
    2025/07/31
    የሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓም አርዕስተ ዜና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ሻረ። የአንጎላ መንግሥት የነዳጅ ዘይት ዋጋ ለመጨመር መወሰኑ በዚህ ሳምንት ባስነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 22 ሰዎች መገደላቸውን አሳወቀ። ጀርመን ለፍልስጤም የመንግሥትነት ዕዉቅና መሰጠት ያለበት የሁለት መንግስታት መፍትሔ ድርድር ሲያበቃ ነው ብላ እንደምታምን አሳወቀች ።ይሁንና እስራኤል በኃይል የያዘችዉን የፍልስጥም ግዛት ለመጠቅላል የእስራኤል ሁለት ሚንስትሮች ያሰሙት ዛቻ የተናጥጠል የዕዉቅና እርምጃ እንድትወስድ ሊያደርጋት እንደሚችል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የሐምሌ 23 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    2025/07/30
    -የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ምክር ቤት ክልሉ ከኦሮሚያ ክልል ጋር በይገባኛል የሚወዛገብባቸዉን አካባቢዎች ይዞታ በተመለከተ በቅርቡ ያሳለፈዉ ዉሳኔ የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎችና የፖለቲካ ፓርቲን ተቃዉሞ ቀስቅሷል። ---የሱዳን ተፋላሚ ኃይላትን ለማደራደር ታስቦ የነበረ የአራት ሐገራት የሚኒስትሮች ስብሰባ በግብፅና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ልዩነት ምክንያት ተሰረዘ።--በረሐብ ለሚሳቃየዉ የጋዛ ሕዝብ የሰብአዊ ርዳታ የጫኑ ከ200 በላይ ካሚዮኖች ዛሬ ከተቀረዉ ዓለም ወደ ተቆራረጠችዉ የፍልስጤሞች ግዛት ገቡ።የአዉሮጳ መንግስታት ደግሞ ለጋዛ ፍልስጤማዉያን ከየር ሰብአዊ ርዳታ ለመጣል እየተዘጋጁ ነዉ።የዜናዉ መልዕክት የእስካሁኑ ነበር።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 22 ቀን 2017 ማክሰኞ
    2025/07/29
    አርስተ ዜና፤--የጀርመኑ መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ መርስ የጀርመን መንግስት ከዮርዳኖስ ጋር በመተባበር ለጋዛ የሰብአዊ ርዳታ በአየር ላይ ለማድረስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናገሩ። በፍልስጤም ግዛት ውስጥ የሚታየዉ ከፍተኛ የምግብ እና የውኃ እጥረት ለአስከፊ ረሃብ እንዳይዳርግ ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች አስጠንቅቀዋል።--በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎችና ባለድርሻ አካላት አገራዊ መግባባትንና ዘላቂ መፍትሔዎችን እንዲያመጡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጠየቀ። ታይላንድ እና ካምቦጂያ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ስምምነቱ ተጥሶ ውጊያ ማገርሸቱ ተሰማ።
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የሐምሌ 21 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    12 分
  • የሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ/ም የዓለም ዜና
    2025/07/27
    DW Amharic-የዛሬው የዓለም ዜና ጥንቅር፤ የአልሸባብ ታጣቂዎች ማሃስ የተባለች ቁልፍ ከተማ መቆጣጠራቸውን፤በጋዛ እየተባባሰ ያለውን ሰብአዊ ቀውስ ለማቃለል የመጀመሪያወቹ የእርዳታ መኪኖች ፍልስጤም ግዛት መድረሳቸውን፤ በግሪክ ከባድ የሙቀት ያስከተለው የሰደድ እሳት አደጋው እየጨመረ መምጣቱን፤ ኢራን ሁለት በስደት ላይ ያለ የታጣቂ ቡድን አባላትን በሞት መቅጣቷን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
    続きを読む 一部表示
    9 分