エピソード

  • DW Amharic የሰኔ 08 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    2025/06/15
    በዶናልድ ትራምፕ የሚመራው የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር ኢትዮጵያን ጨምሮ 36 ሀገራትን የጉዞ ዕቀባ ከጣለባቸው ጎራ የማካተት ዕቅድ አለው ተባለ። በጋዛ ሠርጥ በእስራኤል እና በአሜሪካ ድጋፍ ምግብ በሚታደልበት ቦታ በተከፈተ ተኩስ ስምንት ሰዎች መገደላቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ። እስራኤል እና ኢራን አንዳቸው በሌላቸው ላይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ጨመረ። የጀርመን መራኄ መንግሥት ኦላፍ ሾልስ በቡድን ሰባት ሀገራት ስብሰባ ላይ የእስራኤል እና የኢራንን ግጭት ለማቆም በአራት ጉዳዮች ላይ ከሥምምነት ይደረሳል የሚል ተስፋ እንዳላቸው አስታወቁ። በሰሜናዊ ሕንድ ሔሊኮፕተር ተከስክሶ የሰባት ሰዎች ሕይወት አለፈ።
    続きを読む 一部表示
    8 分
  • የሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2025/06/14
    *ደቡብ አፍሪቃ በጎርፍ አደጋ ቢያንስ 86 ሰዎች ሞቱ *እስራኤል እና ኢራን ውጥረት ቀጥሏል *የአሜሪካ ድምጽ አገልግሎት የፋርስ ቋንቋ ስርጭቱን መልሶ ጀመረ *ከትራምፕ 79ኛ የልደት ቀን ጋር የተገጣጠመው የዩናይትድ ስቴትስ ጦር 250ኛ ዓመት *የሸንገን ስምምነት 40 ዓመት ሞላው *ሩሲያ ተጨማሪ 1,200 የዩክሬን ወታደሮች አስክሬን መለሰች
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የሰኔ 6 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    12 分
  • የሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ,ም የዓለም ዜና
    2025/06/12
    የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ የነበሩትን የአቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስን ያለመከሰስ መብት አነሳ። የአዲስ አበባ ሰበር ሰሚ ችሎት የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የዋስትና መብት እንዲጠበቅ ወሰነ። ከሕንድ ወደ ለንደን ለመጓዝ 242 መንገደኞችን አሳፍሮ የተነሳው አውሮፕላን በደቂቃዎች ውስጥ ተከስክሶ በርካቶች መሞታቸው ተሰማ። የአውሮጳ ሕብረት ኢራን የኒኩሊየር ጦር መሳሪያ እንዳይመረት የሚያግደዉንና የተቀበለችዉን ግዴታ እንድታከብር ጠየቀ።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የሰኔ 4ቀን 1017 የዓለም ዜና
    2025/06/11
    -መቀሌ ዉስጥ ዛሬ አደባባይ የተሰለፉ የትግራይ ተፈናቃዮች የክልሉ ፕሬዝደንት ፅሕፈት ቤት የሚገኝበትን ቅጥር ግቢ ጥሰዉ ገቡ።ከቤት ንብረታቸዉ የተፈናቀሉ ነዋሪዎች ወደቀያቸዉ እንዲመለሱ በተደጋጋሚ በአደባባይ ሠልፍ እየጠየቁ ነዉ።---የኢትዮጵያ መንግስት የሕግ ሒደትንም ሆነ የፕሬስ ነፃነትን እንደማያከብር ሁለት የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶች አስታወቁ።--ዩናይትድ ስቴትስ ኢራንን ካጠቃች የኢራን ጦር መካከለኛዉ ምሥራቅ የሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሠፈሮችን እንደሚመታ የኢራን መከላከያ ሚንስትር አስጠነቀቁ።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    11 分
  • የሰኔ 2 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2025/06/09
    መቐለ፥ ሕወሓት የፌዴራል መንግሥቱን በበርካታ ጉዳዮች ከሰሰ፤ ባሕርዳር፥ የማዳበሪያ ዋጋ ማሻቀብ በዋና ዋና ሰብሎች ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል፤ ዋሽንግተን፥ 12 አገራት ላይ የተጣለው የጉዞ እገዳ መተግበር ጀመረ፤ የሎስ አንጀለስ አመጽ የተቀላቀለበት የተቃውሞ ሰልፍ፤ ሩስያ ሌሊቱን ዩክሬንን በመጠነ ሰፊ የድሮን ጥቃት ደበደበች፤ ጋዛ፥ የእስራኤል ጦር የርዳታ ቁሳቁሶችን በጋዛ ሰርጥ ላሉ ነዋሪዎች የጫነች የተባለች መርከብን አስቆመ
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ/ም የዓለም ዜና
    8 分