エピソード

  • DW Amharic የግንቦት 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2026/05/31
    የጋምቤላ ክልል ፖሊስ “የተለየ የይለፍ ፈቃድ ካልተሰጠ በቀር” ማንኛውም ተሽከርካሪ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት መንቀሳቀስ እንደማይችል አስታወቀ። በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አምስት ሕሙማን ከኢቦላ ማገገማቸውን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድኃኖም ተናገሩ። ኢራን ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው ድርድር የኑክሌር የጦር መሣሪያ ላለመስራት መስማማቷን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። የኢራን ዋና ተደራዳሪ ሞሐመድ ባግኸር ጋሊባፍ ግን “የኢራናውያን መብቶች መከበራቸውን ሳናረጋግጥ አንዳች ሥምምነት አናጸድቅም” ብለዋል።
    続きを読む 一部表示
    8 分
  • የግንቦት 22 ቀን 2018 ፤የዓለም ዜና
    2026/05/30
    የዛሬው የዓለም ዜና፤የአማራ ፋኖ የጣለው የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ገደብ የምርጫ ሥራዉን ስለማስተጎጎሉ የደረሰው መረጃ እንደሌለ ምርጫ ቤርድ ማስታወቁ፣የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የኢቦላ ወረርሽን ወደተቀሰቀሰባት ዲሞክራቲክ ኮንጎ ማምራታቸውን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ መስጠቷን፣ በጀርመን የሙኒክ አውሮፕላን ማረፊያ አጠራጣሪ ድሮን መታየቱን ተከትሎ ለአጭር ጊዜ በረራ መቋረጡን አሜሪካ ስምምነት ላይ ካልደረሰ በኢራን ጦርነቱን እንደገና ለመጀመር ዝግጁ መሆኗን መግለጿን፣እንዲሁምሩሲያ፤ በአርሜኒያ የሚገኙ አምሳደሯን መጥራቷን አካቷል።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/05/29
    ከአማራ ክልል መንገደኞችን ጭኖ ትናንት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ አውቶብስ ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካቶች መገደላቸው ተሰማ። ማዕከላዊ ኬንያ ውስጥ በሚገኘው የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት የተነሳውን እሳት በመለኮስ የተጠረጠሩ ስምንት ተማሪዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በሀገሪቱ በኤቦላ ተሐዋሲ ለተያዙ የአሜሪካ ዜጎች አግልሎ ማቆያ የማዘጋጀት እቅድን በጊዜያዊነት አገደ። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለገባችበት ውዝግብ ለታሰበው የሰላም ስምምነት ከቃል ይልቅ ተግባር እንደምትፈልግ አስታወቀች።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የረቡዕ ግንቦት 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2026/05/27
    አ.አ፥ ለቀጣዩ ምርጫ ሥራ ዝግ እንደሚኾን ምርጫ ቦርድ ዐሳወቀ፤ አ.አ፥ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በመላ ኢትዮጵያ ተከበረ፤ ጆሐንስበርግ፥ የጋና መንግሥት ዜጎቹን መጤ ጠል ሥጋት ካጠላባት ደቡብ አፍሪቃ ወደ አገራቸው እየመለሰ ነው፤ ዋሽንግተን፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ናይሮቢ፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ጋዛ፥እሥራኤል አዲስ የተሾሙ የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥን መግደሏን ዐሳወቀች፤
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2026/05/28
    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በጥሞና ወቅት “ፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ” ከለከለ። ክልከላው የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያግዛል በተባለው የጥሞና ጊዜ ከማይደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተካተተ ነው። ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚዋጋው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል “ለተከታታይ አምስት ቀናት ከአንቡላንሶች በስተቀር ሁሉም መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ መደረጋቸውን” አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት አገሪቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ያደረገው ውይይት ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓም የዓለም ዜና
    2026/05/26
    የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና በሱዳኑ ጦርነት ከፈጥኖ ደራሹ ኃይል በምህጻሩ RSF ጎን ተሰልፈው የሚዋጉ ኮሎምብያውያን የግል ቅጥረኛ ወታደሮችን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ታሰለጥናለች ሲል ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታወቀ ። በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እጎ ዩጋንዳ ዉስጥ ተጨማሪ ሰዎች በኢቦላ ተሕዋሲ መያዛቸዉን የሁለቱ ሐገራት የጤና ባለሥልጣናት አስታወቁ። ኢራን፣ ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት የፈጸመችባትን የአየር ድብደባ አወገዘች። ድብደባዎቹን የተኩስ አቁሙን የጣሰ ሲል ያወገዘው የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ ጥቃቶቹ ለሚያስከትሉት መዘዞች ሁሉ ዋሽንግተን ሃላፊነቱን እንደምትወስድ አስጠንቅቋል።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/05/25
    መገናኛ ብዙኃን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በመንግሥት ቁጥጥር ስር በሆነበት፤ አመጽና ዛቻን በመጋፈጥ፤ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ እንደሚሳተፉ ተዘገበ። ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልእኮ የወታደሮች ቁጥር በመቀሱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አንድ ጥናት አመለከቱ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነቱን ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር የምታካሄደው ድርድር መሻሻሎች ቢኖሩትም ስምምነት ላይ ገና አልተደረሰም አለች። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ከኢራን ጋር የሚደረገው ስምምነት ወይ ታላቅና ትርጉም ያለው ይሆናል ወይ ደግሞ ስምምነት አይኖርም ብለዋል።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
    2026/05/24
    • በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 204 ደረሰ። ኢትዮጵያን ጨምሮ 10 የአፍሪካ ሀገራት ወረርሽኙ አስግቷቸዋል። • አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸው ተሰማ። • ሩሲያ ዛሬ ሌሊት በዩክሬን መጠነ-ሰፊ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት “ኦሬሽኒክ” የተሰኘውን የሃይፐርሶኒክ ባሊስቲክ ሚሳኤል • በፓኪስታን በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት የ23 ሰዎች ህይወት አለፈ። • ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ዛሬ ደቡብ አፍሪቃ ኬፕታውን ውስጥ የተደረገውን የማራቶን ሩጫ የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፉ ።
    続きを読む 一部表示
    8 分