エピソード

  • የሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/07/02
    በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ኮሬ ዞን ተማሪዎች እስካሁን የዓመቱን የማጠቃለያ ፈተና እንዳልተፈተኑ ወላጆች ገለጹ። መምህራኑ «መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለመደጎም ያደረገው ውዝፍ የደመወዝ ጭማሪ በተሟላ ሁኔታ አልተከፈለንም» በሚል ወደ ትምህርት ቤት አልሄዱም ተብሏል። በሰሜናዊ ናይጀሪያ ማለቂያ ባጣው ግጭት ምክንያት ታይቶ የማይታወቅ ረሀብ መከሰቱን ዛሬ የተመድ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በስምንት ተማሪዎች ላይ የግድያ ክስ መሰረተ። ዛሬ ማለዳ ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 21 ሰዎች መገደላቸውን የከተማዋ ከንቲባ አመለከቱ። 86 ሰዎችም ተጎድተዋል።
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/07/01
    የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. አርእስተ ዜና አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የሱዳኑን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በምህጻሩ RSFን በሰብዓዊነት ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎችና በዘር ማጥፋት ወንጀል ከሰሰ ። ትውልደ-ኢትዮጵያዊቷ ሶሻል ዴሞክራት ሜላት ኪሮስ ትናንት ማክሰኞ በአሜሪካ በዴንቨር አካባቢ የተካሄደውን ምርጫ አሸነፉ። ሜላት ኪሮስ ለ15 ጊዜ የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑትን ዲያና ደጌትን ነew ያሸነፉት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን በቀጠር ዋና ከተማ ዶሀ ዛሬ ቀጥተኛ ያልሆነ ንግግር መጀመራቸው ተሰምቷል ።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/07/23
    የሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በሚገኘው አባይ ገዳመ አስቄጤስ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ላይ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተፈፀመ በተባለ የድሮን ጥቃት የ2 መነኮሳት ህይወት ማለፉን የገዳሙ አበምኔትና የወረዳዉ ቤተክህነት ኃላፊ ተናገሩ። በኢራን የሚደገፉት የሁቲ አማጽያን ዛሬ ቀይ ባህር ላይ በነበሩ ሁለት የሳዑዲ አረብያ ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ተናግረዋል። ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ትናንት የተፈራረሙት ስምምነት ሳዑዲ አረብያ ከእስራኤል ጋር መደበኛ ግንኙነት እንዲኖራት የሚጠይቅ መሆኑን ትራምፕ አስታወቁ።
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የሰኔ 26 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2026/07/03
    -በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዘይሴ ወረዳ የመንግሥት ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት 10 ሰዎች መገደላቸዉን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) አስታወቀ።---የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አ,ያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ አስከሬን የሽኝት ሥርዓት ዛሬ ቴሕራን ዉስጥ ተጀመረ።ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት ዕለት ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ የተገደሉት ኻምኔይ ኢራንን ለ37 ዓመት መርተዋል።86 ዓመታቸዉ ነበር።--ሐሙስ ይቀበራሉ።-የጀርመን የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዩሊያን ናግልስ ማን በከፍተኛ ግፊት ሥልጣኑን ለቀቀ።
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓለም ዜና
    2026/07/04
    በዛሬው የዓለም ዜና ፤ የትግራይ ክልል አሁን ያለበት ሁኔታ አሳስቦኛል ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መግለፁን፣የአውሮፓ እና የአሜሪካ መሪዎች ስደተኞችን ለመጠበቅ እና ለማዋሃድ የበለጠ እንዲሰሩ የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳሥ ማሳሰባቸውን፣ኢራን ለሟቹ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊካሜኒ ብሄራዊ የሽኝት ሥነ ስርዓት ዛሬ በይፋ መጀመሯን፣ጀርመን፤ ቤጂንግ የሩሲያ ወታደሮችን ማሰልጠኗን የሚያሳዩ ዘገባዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቻይናን ማስጠንቀቋን፣አማራጭ ለጀርመን የተባለው መጤ ጠል ፓርቲ ዛሬ መሪዎቹን መምረጡን እንዲሁም ዶናልድ ትራምፕ ለ11 ተከሳሾች ይቅርታ ማድረጋቸውን የሚያስቃኙ ዜናዎች ተካተዋል።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • DW Amharic-የሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓለም ዜና
    2026/07/05
    በዛሬው የዓለም ዜና በቀይ ባሕር ትቀዝፍ የነበረች አንዲት ዕቃ ጫኝ መርከብ በየመን ሁዴይዳ የባሕር ክልል አካባቢ ጥቃት ተፈፀመባት መባሉን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ በሂዝቦላህ ላይ የምታካሂደውን ዘመቻ አጠናክራ እንደምትቀጥል መግለጿን፣በእስራኤል እስር ቤት ውስጥ የሚገኙት የጋዛ ሆስፒታል ዳይሬክተር ህይወታቸው አደጋ ላይ ወድቋል መባሉን፣ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው የአያቶላህ አሊ ካማኔይ የሀዘን ሥነ ሥርዓት ላይ ልጆቻቸው እና ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት መገኘታቸውን እንዲሁም ትራምፕ በአሜሪካ 250ኛ ዓመት የነፃነት በዓል ባደረጉት ንግግር የሀገር ፍቅርን ከፓርቲ ፖለቲካ ጋር ቀላቅለዋል በሚል መተቸታቸውን አካቷል።
    続きを読む 一部表示
    8 分
  • DW Amharic የሰኔ 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2026/07/06
    የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት የ15 ዓመት አዳጊዎችን ጨምሮ ሲቪል ሰዎችን እያፈኑ በግዳጅ ለውትድርና በመመልመል ላይ እንደሚገኙ ሒውማን ራይት ዎች ወነጀለ። በሱዳን እየተካሔደ በሚገኘው ጦርነት በስድስት ወራት ብቻ 330 ሕጻናት መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት አስታወቀ። ሐማስ የጋዛን መንግሥታዊ መዋቅር መፍረሱን አስታወቀ። የዩክሬን ጦር ኦምስክ በተባለ ግዙፉ የሩሲያ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት ፈጸመ። ለጀርመን ለሚቀጥለው ዓመት የ555.4 ቢሊዮን ዩሮ ረቂቅ በጀት ጸደቀ። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ከኢራን ጋር ከሥምምነት ላይ ካልደረሰች አገራቸው የጀመረችውን ጦርነት "እንጨርሰዋለን" ሲሉ ዛቱ
    続きを読む 一部表示
    12 分
  • የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓም ረቡዕ
    2026/07/08
    አርስተ ዜና፤ የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስና ወታደራዊ ኃይል በጆሃንስበርግ አቅራቢያ በሕገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ሥራዎች ላይ ባደረጉት ከፍተኛ ዘመቻ ከ200 በላይ ሰዎችን አሰሩ። በደቡብ አፍሪቃ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን መካከል ህጋዊ ወረቅት የሌላቸዉ ስለመያዝ አለመያዛቸዉ እስካሁን የወጣ ግልፅ መረጃ የለም።-የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኔቶ ስብሰባ አንካራ ተገኝተዋል። ትራምፕ ድርጅቱ ባሳየዉን ወታደራዊ ኤግዚቢሽን የተደሰቱ አይመስልም። የአውሮጳ ህብረት ሀገራት ኔቶን ለማጠናከር የሚያደርጉትን ጥረትና የኢራን ጦርነት ለመቀላቀል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ትራምፕ በተደጋጋሚ ተችተዋል።
    続きを読む 一部表示
    11 分