『የዓለም ዜና』のカバーアート

የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

著者: DW
無料で聴く

このコンテンツについて

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።2025 DW 政治・政府
エピソード
  • የታኅሣሥ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2025/12/21
    ወደ ጋምቤላ በቂ የጸጥታ አካላት በአስቸኳይ እንዲሰማሩ ኢሰመኮ አሳሰበ ፤ ደቡብ አፍሪቃ ፤ ቢያንስ ዘጠኝ ሰዎች በታጣቂዎች ጥቃት ተገደሉ ፤ የእስራኤል ካቢኔ እስራኤል በኃይል በያዘችው የፍልስጤም ግዛት የዮርዳኖስ ወንዝ ምዕራባዊ ዳርቻ 19 አዳዲስ የሰፈራ መንደሮች እንዲቋቋሙ አፀደቀ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ከቬንዙዌላ የባህር ዳርቻ ለሁለተኛ ጊዜ ድፍድፍ ዘይት የጫነ መርከብ በቁጥጥሯ ስር አዋለች፤
    続きを読む 一部表示
    9 分
  • DW Amharic የታኅሳስ 11 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2025/12/20
    የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር ካሚል ዒድሪስ ጦርነት በሚካሔድባቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ርዳታ በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ ከተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ሌሎች ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር ወደ ኒው ዮርክ አቀኑ። የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ቦላ ቲኑቡ የሀገራቸውን የጸጥታ ተቋማት በከፍተኛ ሁኔታ ለማጠናከር ቃል ገቡ። አንድ ኤርትራዊን ጨምሮ አራት ሰዎች ባለፈው አንድ ሣምንት በዩናይትድ ስቴትስ የፍልሰት እና የጉምሩክ መስሪያ ቤት በእስር ላይ ሳሉ መሞታቸውን የሀገሪቱ መንግሥት መረጃ ይፋ አደረገ። የአፍሪካ ዋንጫ የእግር ኳስ ጨዋታ ከጎርጎሮሳዊው 2028 በኋላ በየአራት ዓመቱ እንደሚካሔድ ተወሰነ።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የታኅሳስ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2025/12/19
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ በአዲስ አበባ ተገናኙ። በኢትዮጵያ ለስደተኞች የሚደረገው ድጋፍ ከውድቀት አፋፍ እንደሚገኝ መንግሥት እና አራት ድርጅቶች አስጠነቀቁ። በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ሊባባስ እንደሚችል የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባልደረባ ሥጋታቸውን ገለጹ። ስዊድን በኤርትራ ላለፉት 24 ዓመታት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅ በሕይወት እንዳለ ገለጸች። የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ቋሚ የአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ በዕጣ የሚያገኙበትን የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም ሊያቆም ነው።
    続きを読む 一部表示
    12 分
まだレビューはありません