『የዓለም ዜና』のカバーアート

የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

著者: DW
無料で聴く

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።2026 DW 政治・政府
エピソード
  • የግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/05/25
    መገናኛ ብዙኃን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በመንግሥት ቁጥጥር ስር በሆነበት፤ አመጽና ዛቻን በመጋፈጥ፤ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ እንደሚሳተፉ ተዘገበ። ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልእኮ የወታደሮች ቁጥር በመቀሱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አንድ ጥናት አመለከቱ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነቱን ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር የምታካሄደው ድርድር መሻሻሎች ቢኖሩትም ስምምነት ላይ ገና አልተደረሰም አለች። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ከኢራን ጋር የሚደረገው ስምምነት ወይ ታላቅና ትርጉም ያለው ይሆናል ወይ ደግሞ ስምምነት አይኖርም ብለዋል።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
    2026/05/24
    • በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 204 ደረሰ። ኢትዮጵያን ጨምሮ 10 የአፍሪካ ሀገራት ወረርሽኙ አስግቷቸዋል። • አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸው ተሰማ። • ሩሲያ ዛሬ ሌሊት በዩክሬን መጠነ-ሰፊ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት “ኦሬሽኒክ” የተሰኘውን የሃይፐርሶኒክ ባሊስቲክ ሚሳኤል • በፓኪስታን በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት የ23 ሰዎች ህይወት አለፈ። • ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ዛሬ ደቡብ አፍሪቃ ኬፕታውን ውስጥ የተደረገውን የማራቶን ሩጫ የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፉ ።
    続きを読む 一部表示
    8 分
  • የግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2026/05/23
    ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ኡጋንዳ በተጨማሪ 10 የአፍሪካ ሐገራት የኢቦላ ቫይረስ ሥርጭት እንደሚያሰጋቸው የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ ድርጅት አስታወቀ። ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ዳግም ጦርነት የምታውጅ ከሆነ ብርቱ አጸፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ኢራን አስጠነቀቀች። በሰሜን ቻይና በምትገኝ የሻንዚ ግዛት በአንድ የከሰል ማዕድን ማውጫ ትላንት ባጋጠመ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 90 መድረሱን ተሰማ። ዩክሬይን በሩስያ ቁጥጥር ሥር በሚገኘው እና የቀድሞ ግዛቷ በነበረው ሉጋንስክ ከተማ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃት 18 ሰላማዊ ሰዎች ሲሞቱ 48 መቁሰላቸውን የአካባቢው የሩስያ ገዢ አስታወቁ።
    続きを読む 一部表示
    10 分
adbl_web_anon_alc_button_suppression_c
まだレビューはありません