-
サマリー
あらすじ・解説
የሚያዚያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ትናንት ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የሚሊሻ አባላትን ጨምሮ 15 ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ በጥቃቱ ከባድ መሣሪያዎችም ጥቅም ላይ መዋላቸውንም ለዶቼቬለ ተናግረዋል። ጅቡቲ ሕገ ወጥ ስደተኞችን በቅርቡ ማባረር እንደምትጀምር አስታወቀች። ስደተኞቹ እስከሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አዟል። የፍልስጤም ፕሬዝዳንት መሐሙድ አባስ ሀማስ ጋዛ ውስጥ የያዛቸውን ታጋቾች በሙሉ እንዲለቅ ጠየቁ። ታጋቾቹን ይዞ መቆየቱ እስራኤል በፍልስጤም ጥቃቷን እንድትቀጥል ሰበብ ሆኗታል ብለዋል።