『ዜና መጽሔት』のカバーアート

ዜና መጽሔት

ዜና መጽሔት

著者: DW
無料で聴く

このコンテンツについて

በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።2025 DW 政治・政府
エピソード
  • የግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2025/06/04
    የዜና መፅሔት ጥንቅራችን ኢትዮጵያና ኤርትራ ዳግም ጦርነት ይገጥሙ ይሆናል የሚለዉን ሥጋት ከምልክቶቹ ጋር ያሰባጠረዉን ዘገባ ያስቀድማል።አንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በተፈናቃዮች አያያዝ ምክንያት የኢትዮጵያ መንግሥት ለመክሰስ ማቀዱን የሚዳስሰዉ ዘገባ ተከትሎ፣የኢትዮጵያ ዉስጥ ቴክኒክና ሙያ የሚያጠኑ ተማሪዎች ቁጥር ማሽቆልቆሉን የሚያወሳዉ ያሰልሳል።ዜና መፅሔቱ የጋምቤላ የወርቅ ምርት መጨመሩን የሚቃኝ ዘገባዉ አለዉ።
    続きを読む 一部表示
    19 分
  • የግንቦት 26 ቀን 2017 ዜና መፅሔት
    2025/06/03
    በዜና መጽሔት ጥንቅሩ፤ የህወሓት አመራሮች ካለፈ ጦርነት ያላገገመች ትግራይን ዳግም ወደሌላ ጥፋት ከሚያስገባ አካሄድ ይቆጠቡ ሲል ተቃዋሚው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ መግለጫ ማዉጣቱ።የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለሚያሰባስባቸው የምክክር አጀንዳዎች ጥንቃቄ እንዲያደርግ ሲል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መጠየቁ፡፡ለሳምንት ወደ ትግራይ እንዳይጓዙ ተከልክለው የነበሩ ሸቀጥ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ጉዟቸው እንዲቀጥሉ ተፈቀዳላቸዉ መባሉ ፤ እንዲሁም ከነገ በስትያ ለጉብኝት ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የሚያቀኑት አዲሱ የጀርመን ቻንስለር የጉብንት አንድምታ የተሰኙ ርዕሶችን በስፋት እናያለን
    続きを読む 一部表示
    18 分
  • የዜና መጽሔት፤ ግንቦት 25 ቀን 2017 ሰኞ
    2025/06/02
    7ኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ"አስቻይ" የፀጥታ "ሁኔታዎች" ባሉባቸው ባላቸው የምርጫ ክልሎች እንደሚያከናውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቋል። ሀገራዊ ምክከር ኮሚሽን ከፌደራል መንግስት ከማህበራት ተወካዮች ከታዋቂ ሰዎችና ከሌሎችም የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ለሶስት ቀናት ያካሄደውን የምክክርና የአጀንዳ ማሰባሰብ መርሃ ግብር አብቅቷል። በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ውስጥ በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት 6 የኃይል ተሸካሚ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በመውደቃቸው ካለፈው ሳምንት መጨረሻ አንስቶ ወደ ሱዳን የሚተላለፈውን ጨምሮ በዞኑ አብዛኛዎቹ ከተሞች ኤሌክትሪክ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።
    続きを読む 一部表示
    14 分

ዜና መጽሔትに寄せられたリスナーの声

カスタマーレビュー:以下のタブを選択することで、他のサイトのレビューをご覧になれます。