エピソード

  • ማኅደረ ዜና፤ ውጥረት ያልተለየው የአፍሪቃ ቀንድ ወቅታዊ ኹኔታ
    14 分
  • ሶሪያ፤ አንድ አመት ክበሺር አላሳድ በኋላ
    9 分
  • የደቡብ አፍሪካ እና አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ፍጥጫ ያየለበት የቡድን 20 ጉባኤ
    2025/11/24
    የቡድን 20 ጉባኤ ሲጠናቀቅ በሱዳን፣ ኮንጎ፣ በእስራኤል በጉልበት በተያዙት የፍልስጤም ግዛቶችና በዩክሬን “ፍትኃዊ፣ ሁሉን አቀፍና ዘላቂ ሰላም” እንዲወርድ እንደሚሠሩ መሪዎቹ ቃል ገብተዋል። በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሔደው ጉባኤ የደቡብ አፍሪካ እና የአሜሪካ ውዝግብ ተጭኖታል። ጉባኤው ሲጠናቀቅ አሜሪካ ቀጣይ ፕሬዝደንትነቱን አልተረከበችም።
    続きを読む 一部表示
    14 分
  • ማሕደረ ዜና፣ የትራምፕ ተቃራኒ የአፍሪቃ መርሕ
    2025/11/17
    አንዳዶቹ ፎቶ ግራፎች ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዉስጥ የተነሱ መሆናቸዉ ቢረጋገጥም የነጮችን የበላይነት ለማስከበር ቆርጠዉ የተነሱት ዶናልድ ትራምፕ ግን ነጭ ደቡብ አፍሪቃዉያን ወደ አሜሪካ እንዲሰደዱ ፈቀደዋል።አሜሪካ ጥግ የምትገኘዉን የጃማይካ ስደተኛን ሳይቀር ከአሜሪካ ወደ አፍሪቃ ያስግዛሉ።መሰደድ የማይፈልጉትን የደቡብ አፍሪቃ ነጭ ዜጎችን ወደ አሜሪካ ይጋብዛሉ።ከአፍሪቃ ጋር የንግድ ግንኙነትን ማጠናቀር እሻለሁ ይላሉ፤ ደቡብ አፍሪቃን በዘረኝነት ያወግዛሉ።
    続きを読む 一部表示
    14 分
  • ማሕደረ ዜና፣ የኢትዮጵያ-ኤርትራ ምድር ሌላ ጦርነት እየተደገሰለት ይሆን?
    2025/11/10
    ኢትዮጵያ በየሥፍራዉ ከሚደረጉ ግጭቶች በተጨማሪ የኑሮ ዉድነት፣ ሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ደሕንነት እጦት፣ እገታና ግድያን የመሳሰሉ የሕግና ሥርዓት መጓደሎች አቃርጠዉ እንደያዟት ነዉ።ትግራይን ጨምሮ ከአራት ሚሊዮን የሚበልጥ ተፈናቃይ በየመጠለያ ጣቢያዉ እንደሰፈረ ነዉ።የኤርትራ ሁኔታም ከኢትዮጵያ የባሰ እንጂ ያነሰ አይደለም።በዚሕ ላይ አካባቢዉ ሌላ ጦርነት ይችል ይሆን?
    続きを読む 一部表示
    13 分
  • የማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2025/11/04
    ፓሪስ፥የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ያስተዋወቀ መድረክ ተከናወነ፣ ዴንሐግ፥ በሰዎች ማዘዋወር የተጠረጠረ ኤርትራዊ ላይ ኔዘርላንድስ ውስጥ ክስ ተከፈተ፣ ካርቱም፥ የሱዳን ተፋላሚ ኃይላት ለዕርቅ አወንታዊ ምላሽ መስጠታቸውን የትራምፕ ረዳት ተናገሩ፣ ዳርኤሰላም፥ ፖሊስ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ተጠቃሚዎች የሚረብሹ ምስሎች እንዳይጋሩ አስጠነቀቀ፣ ቤርሊን፥ ጀርመን በሚቀጥለው የጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በ2026 ለዩክሬይን የምትሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ ለማሳደግ ወሰነች
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • ማሕደረ ዜና፣ ኤል ፋሻር-የሱዳን እልቂት አዲስ ምዕራፍ
    2025/11/03
    የካይሮና የአቡዳቢ ገዢዎች የመንንን ለመደብደብ ጥብቅ ወዳጅ ነበሩ።ቀጠር በማዕቀብ ለመቅጣት ተባባሪ ነበሩ።የቀድሞዉን የሶሪያ መሪ በሽር አል አሰድን ለማስወገድ ተመሳጣሪ ነበሩ።ሱዳንና ሊቢያ ጦርነት ላይ ተቃራኒ ኃይላትን ይደግፋሉ።ሱዳንም የቀድሞ ወዳጆች የገጠሙት-ወዳጆችን ያቃረነ ጦርነት ማዕከል እንደሆነች ቀጥላለች።
    続きを読む 一部表示
    18 分
  • ማሕደረ ዜና፣ የASEAN ጉባኤ፣ የትራምፕ ጉብኝትና የሲኖ-አሜሪካ ድርድር
    2025/10/27
    ቤጂንጎች ሲያመሩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ «የንግድ ጦርነት ቀላል ነዉ አልኩ እንጂ---ከቻይና ጋር ማለቴ አልነበረም» ማለታቸዉ ተዘገበ።ዘ-ኤኮኖሚስት የተሰኘዉ መፅሔት ደግሞ በቀደም «ቻይና በትራምፕ ዱላ አሜሪካናንን ደበደበች» አለ።የሁለቱ ሐገራት የንግድና የኤኮኖሚ ባለሥልጣናት ሰሞኑን ለ5ኛ ዙር እየተደ,ራደሩ ነዉ።የቻይና ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ጉዮ ጂያኩን ዛሬ እንዳሉት ዉይይቱ የሰከነና መግባባት የታየበት ነዉ።
    続きを読む 一部表示
    14 分